አንጋፋው የስፖርት ሰው ፍቅሩ ኪዳኔ አረፉ
ጥቅምት 1/2015 (ዋልታ) በስፖርት ጋዜጠኝነት፣ አመራርነት እና ደራሲነት የሚታወቁት አንጋፋው የስፖርት ሰው ፍቅሩ ኪዳኔ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
በኢትዮጵያ የስፖርት ጋዜጠኝነት ታሪክ ፈር ቀዳጅ ከሚባሉ ግለሰቦች አንዱ እንደነበሩና የእግር ኳስ ጨዋታን በቀጥታ በሬዲዮ በማስተላለፍ የመጀመርያው ኢትዮጵያዊ መሆናቸው ይነገራል፡፡
ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ በተለያዩ ቋንቋዎች የስፖርት ዘገባዎችን በማቅረብ፣ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ በካፍ እና በኦሎምፒክ ኮሚቴ አመራርነት፣ በጋዜጠኞች ማህበር መስራችነት እና አመራርነትም ከፍተኛ ግልጋሎት ሰጥተዋል።
“የፒያሳ ልጅ” በተሰኘው መጽሐፋቸው እና ሌሎች መጻሕፍቶችም ከፍተኛ እውቅና ያገኙ ደራሲ እንደነበሩ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን መረጃ አመላክቷል፡፡
የዋልታ ሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ኮርፖሬት በአንጋፋው የስፖርት ሰው ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰባቸው፣ ለሙያ ባልደረቦቻቸው እና ለስፖርት ቤተሰቡ መፅናናትን ይመኛል።
— Sahle-Work Zewde (@SahleWorkZewde) October 12, 2022
ጋሽ #FekrouKidane quintessential man #Ethiopia has given to🌐. He travelled over 180 countries inspiring #peace through #sport.
— Wondwosen (Wondy) Asnake Kibret (@WondyAK) October 11, 2022
Story teller, full of love, laughter & generosity.
Didn’t miss a birthday or baptism of your child.
We❤️& miss you so much. RIP @SahleWorkZewde @UN pic.twitter.com/ogJuQV46T8
ጋሽ #FekrouKidane forever be remembered 4 his consistent voice for @UN to use sport as a tool for development around the world.
— Wondwosen (Wondy) Asnake Kibret (@WondyAK) October 11, 2022
Tonight, I am sad we lost an amazing human being, but those of us inspired & mentored by him will carry on his work. @antonioguterres @sebcoe @iocmedia pic.twitter.com/kngawUMC1P
#AFCON started 60 yrs ago today. A reporter covering the event (w/ help of future CAF leader Tessema) tells @bbcafrica about a different era pic.twitter.com/z5v9gN1uO3
— Piers Edwards (@piers_e) February 10, 2017
Biographie of Fékrou Kidane at ICV