በመላው ዓለም የሚኖሩ ውድ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልድ ኢትዮጵያዊያን ከኤፕሪል 20 እስከ ጁለይ 17 ቀን 2022 ድረስ በሚካሄደው የ”Eid to Eid-Homecoming” ዝግጅት ተሳታፊ እንዲሆኑ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በተደረገው ጥሪ መሰረት በስዊዘርላንድ፣ በኦስትሪያ፣ ሀንጋሪ እና በሩሜኒያ ያላችሁ ውድ ወገኖቻችን የፕሮግራሙ ተሳታፊ እንዲሆኑ በአክብሮት ተጋብዛችኋል::


ከኢድ እስከ ኢድ ወደ ሀገር ቤት ጉዞን ተከትሎ የተዘጋጁ መርሀ ግብሮችን በቅርቡ ይፋ ማድረጋችን ይታወሳል። በመርሀ ግብሮቹ ላይ መሳተፍ የሚፈልጉ ከሆነ አስቀድመው መመዝገብ እንዳለብዎት ልናስታውሶት እንወዳለን።
በመሆኑም ቀጥሎ የቀረበውን ሊንክ በመጫን መሳተፍ ለሚፈልጉባቸውን ሁነቶች እንዲመዘገቡ እንጋብዛለን።